የአማራ ባንክ እና ቪዛ፣ በኢትዮጵያ የዲጂታል ክፍያ ስርዓትን ለማሻሻል በትብብር ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ፈፀሙ።

Home / Agreements / የአማራ ባንክ እና ቪዛ፣ በኢትዮጵያ የዲጂታል ክፍያ ስርዓትን ለማሻሻል በትብብር ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ፈፀሙ።

አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ መጋቢት 16 ቀን 2018 ዓ.ም የአማራ ባንክ እና ቪዛ በኢትዮጵያ የዲጂታል ክፍያ ስርዓትን ለማዘመንና ለማሻሻል የሚያስችል ስትራቴጂካዊ አጋርነት መፈፀማቸውን አስታውቀዋል።

ይህ ስምምነት በኢትዮጵያ ውስጥ የዲጂታል ክፍያ አገልግሎቶችን ለማሻሻል እና የፋይናንስ ተደራሽነትን ለማስፋት
እንደሚያስችል
ተገልጿል።

ስምምነ መሠረት፣ አማራ ባንክ የቪዛ ዓለም አቀፍ አውታረ መረብ፣ የደህንነት ደረጃዎችን ቴክኖሎጂ በመጠቀም የካርድ አገልግሎቱን እንዲያስፋፋ እና የዲጂታል ክፍያ መሠረተ ልማቱን እንዲያበረታ ያግዛል።

በዚህ አጋርነት ስምምነት መሠረት፣ ባንኩ ቪዛ የቅድመ ክፍያ (Prepaid) የጎልድ እና ፕላቲኒየም ካርዶች እንዲሁም የዴቢት ካርዶችን በማቅረብ ደንበኞች ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያላቸውን የክፍያ ካርዶችን እንዲጠቀሙ ያስችላል። ይህም በአገር ውስጥና በዓለም አቀፍ የግብይት ሂደት በከፍተኛ መጠን ለማሳደግ ይረዳል ተብሏል

ከዚህ በተጨማሪ፣ አጋርነቱ የፋይናንስ ስርዓትን ለማጠናከር ሚያግዝ ሲሆን፣ ቪዛ ለአማራ ባንክ ስትራቴጂያዊ ምክር፣ የአደጋ ስጋት፣ የማጭበርበር መቆጣጠሪያ ቴክኖሎጂዎች እና የፕሮጀክት አመራር ድጋፍ እንዲሁም ከፍተኛ የደህንነት ደረጃዎች ለማረጋገጥ የሚያስችሉ መፍትሄዎችን ለማቅረብ
ያግዛል

በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የአማራ ባንክ ተጠባባቂ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ እሸቴ የማታይህ ቪዛ ጋር የተፈጠረው ትብብር ባንካችንን ዲጂታል የታገዘ ባንክ ለማድረግ ምንጓዘው ጉዞ ውስጥ ወሳኝ እርምጃ ነው፤ ደንበኞቻችንን ወደ ዓለም አቀፍ ኢኮኖሚ ለማስገባት እና ጥሬ
ገንዘብ አልባ ማህበረሰብ ለመገንባት እንደሚያግዝ እንረዳለንብለዋል።

በተመሳሳይ፣ ቪዛ የምስራቅ አፍሪካ ኃላፊ
እና የኢትዮጵያ ካንትሪ ዳይሬክተር
አቶ ያሬድ እንዳለ በንግግራቸውቪዛ በኢትዮጵያ የዲጂታል ክፍያዎችን እድገት ለመደገፍ ቁርጠኛ ነው፤ አማራ
ባንክ
ጋር ያለው አጋርነት ለደንበኞች የበለጠ ደህንነት ያለውና ቀላል የክፍያ አማራጮችን ለማቅረብ ያግዛልብለዋል።

በእለቱ ባንኩ ከቪዛ ጋር ያደረገው ስምምነት ከኢትዮጵያ የብሄራዊ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ ጋር የተጣጣመ ሲሆን፣ የፋይናንስ ተደራሽነትን ለማስፋትና የባንክ አገልግሎትን ለማዘመን ያስችላል። በተጨማሪም በቀጣይ ዘመን 24/7 የክፍያ አገልግሎት ለደንበኞችና ለንግ
ማህበረሰብ
ለማቅረብ የሚያስችል መሠረት ይፈጥራል።

አማራ
ባንክ
በኢትዮጵያ ውስጥ ፈጣን እድገት እያሳየ ያለ የፋይናንስ ተቋም ሲሆን፣ ዘመናዊ እና ደንበኛ ተኮር አገልግሎቶችን በማቅረብ ለግለሰቦችና ለንግ የፋይናንስ አቅምን ለማሳደግ ያለመ ተቋም
ነው።

ቪዛ በዓለም 200 በላይ አገራት ውስጥ የዲጂታል ክፍያ አገልግሎት የሚያቀርብ ዓለም አቀፍ መሪ ኩባንያ ሲሆን፣ ተስማሚ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ፈጠራ ያለው የክፍያ መስመር በመጠቀም ኢኮኖሚ እንዲያድ በመስራት ላይ ያለ ተቋም ነው

Download ABa Mobile Banking

Download the app and join our digital world.

Copyright© 2026 Amhara Bank S.C. | All Rights Reserved

wpChatIcon
wpChatIcon